ማሕደረ ዜና፣62ኛዉ የሙኒክ የፀጥታ ጉባኤ፣የአዉሮጳ አሜሪካኖች ልዩነት መድረክ
16 February 2026

ማሕደረ ዜና፣62ኛዉ የሙኒክ የፀጥታ ጉባኤ፣የአዉሮጳ አሜሪካኖች ልዩነት መድረክ

ማሕደረ ዜና

About
የጀርመኑ መራሔ መንግሥት የአሜሪካ ወዳጆቻችን በቀጥታ እንዲረዱት በማለት ለጉባኤተኞች በእንግሊዘኛ ጭምር ያደረጉት ንግግር አዉሮጶች በትራምፕ አስዳደር እርምጃና መርሕ ከመስጋት አልፈዉ መናደድ፣ መቆጣታቸዉን የሚያስረዳ ነዉ።የፈረንሳይና የሌሎች የአዉሮጳ መንግሥታት መሪዎችና ተወካዮችም የፕሬዝደንት ትራምፕ አስተዳደርን በተደጋጋሚ ተችተዋል።አዉሮጳ የራስዋን የመከላከያ ኃይል ማጠናከር እንደሚገባት አሳስበዋልም።