ከፍተኛ ሙቀት የበረታባት ድሬደዋ ከተማ የውኃ እጥረት እየተፈታተናት እንደሚገኝ ነዋሪዎች ገለጹ
27 June 2026

ከፍተኛ ሙቀት የበረታባት ድሬደዋ ከተማ የውኃ እጥረት እየተፈታተናት እንደሚገኝ ነዋሪዎች ገለጹ

DW | Amharic - News

About
የድሬደዋ ከተማ ከፍተኛ ሙቀት በምታስተናግድበት በዚህ ደረቃማ ወቅት የገጠማት ኃይለኛ የውኃ እጥረት ሕብረተሰቡን ለችግር ዳርጎታል። ሆቴሎች ለሁለት ቀን ብቻ ለሚበቃ አንድ ቦቴ ውኃ 5,500 ብር እየከፈሉ ነው። የከተማው ውኃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣን ሥራ አስኪያጅ መሐመድ ሙሴ በመብራት መቆራረጥ የተከሰተ የፓምፖች መቃጠል ችግሩን እንዳባባሰ ገልጸዋል።