About
የዜና መጽሔት ጥንቅራችን የኢትዮጵያ መንግሥት በአሸባሪነት ከከሳቸዉ ተጠርጣሪዎች 30 ያክሉ የተከሰሱበትን ወንጀል አምነዉ ምሕረት እንዲደረግላቸዉ የቀረበላቸዉን ጥያቄ ዉድቅ ማድረጋቸዉን የሚቃኘዉን ዘገባ ያስቀድማል። ዜና መፅሔቱ ምሥራቅ ወለጋ ዉስጥ የተጠናከረዉ ግጭት ሰዎች መጉዳትና ማፈናቀሉ፣ ከአማራ ክልል ከዋግኽምራ የተፈናቀሉ ሰዎች ርዳታ መማፀናቸዉ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ያጫረተዉን የዉጪ ምንዛሪ የሚያስተነትኑ ዘገቦች አሉት።