የጥር 8 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
16 January 2026

የጥር 8 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
• ከሑመራ ዞን የተፈናቀሉ ሰዎች “ደሕንነታቸው ተጠብቆ በክብር፣ መረጃ ኖሯቸው እና በፈቃደኝነት” ወደ ቀያቸው መመለስ መጀመር አለበት የሚል አቋም አሜሪካ እንዳላት በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ተናገሩ። • በዩጋንዳ ትናንት ሐሙስ በተደረገው እና ዛሬ ውጤቱ ይፋ ይደረጋል ተብሎ በሚጠበቀው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በተቀሰቀሰ ተቃዉሞ በትንሹ አስር ሰዎች ተገደሉ። • አዲሱን የጋዛ የሽግግር አስተዳደር ስራ የሚቆጣጠር ዓለማቀፍ ተቆጣጣሪ ቦርድ ማቋቋማቸውን የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናላድ ትራምፕ አስታወቁ። • በኢትዮጵያ የፊልምና የመዝናኛ ዘርፍ እውቁ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።