
About
-የጀርመን የዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ዮሐን ቫደፉል ኬንያንና ኢትዮጵያን ለመጎብኘት ዛሬ ናይሮቢ ገብተዋል።የጀርመኑ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር በተለይ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር በሚያደርጉት ዉይይት የትግራይን ዉጥረትና የኢትዮጵያንና የኤርትራን አለመግባባት እንደሚያነሱ አስታዉቀዋል።---የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ሐገራቸዉ ግሪንላንድን ለመወስደት ኃይል እንደማትጠቀም አስታወቁ።ግሪንላንድን ለመዉሰድ ግን በድጋሚ ዝተዋል።-----ቻይና፣ ምያንማርና እስራኤል ባለፈዉ የግሪጎሪያኑ ዓመት 2025 ከዓለም ሐገራት ሁሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ ጋዜጠኞች ማሰራቸዉን የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቹ ድርጅት አስታወቀ።