የጥቅምት 7 ቀን 2018 የዓለም ዜና
17 October 2025

የጥቅምት 7 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
-ትግራይ ዉስጥ ለሁለት ዓመት በተደረገዉ ጦርነት ከ152 ሺሕ በላይ የክልሉ ሴቶች መደፈራቸዉን «የትግራይ ጄኖ ሳይድ» የተባለዉ ኮሚሽን አስታወቀ።ኮሚሽኑ በ166 ገፅ በሰነደዉ ጥናቱ በትግራይ ሴቶች ላይ ከተፈፀመዉ አጠቃላይ ፆታዊ ጥቃት 90 በመቶዉን ያደረሱት የኤርትራና የኢትዮጵያ ጦር ኃይላት ባልደረቦች ናቸዉ ይላል።----ባለፈዉ ሮብ የሞቱት የኬንያ የረጅም ጊዜ ዕዉቅ ፖለቲከኛ የራይላ ኦዲንጋ አስከሬን ዛሬ በይፋ ተሸኘ።---የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕና የሩሲያዉ አቻቸዉ ቭላድሚር ፑቲን የዩክሬን ጦርነት ሥለሚቆምበት ብልሐት በቅርቡ ፊት ለፊት ተገናኝተዉ ለመነጋገር ተስማሙ።