
About
-የትግራይ መከላከያ ኃይል የሚባለዉ ወታደራዊ ሥብስብ አባላት የደሞዝና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች እንዲከበሩላቸዉ በመጠየቅ የጀመሩት ተቃዉሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል።ትናንት የመቀሌን ዛሬ ደግሞ ከመቀሌ-አድግራት መንገድን ዘግተዉ ዉለዋል።---የማዳጋስካር ጦር ኃይል የሐገሪቱን የመንግሥትነት ሥልጣን መቆጣጠሩን አስታወቀ።ጦሩ ሥልጣን መያዙን ያስታወቀዉ የተደበቁት ፕሬዝደንት የማዳጋስካርን ፓርላማ መበተናቸዉን ካስታወቁ ከሰዓታት በኋላ ነዉ።---በእስራኤል ጦር ድብደባና በምግብ እጦት ለረሐብ ለተጋለጠ,ዉ የጋዛ ሕዝብ ሰብአዊ ርዳታ ለማቅረብ ሁሉም መተላለፊያዎች እንዲከፈቱ ለጋሽ ድርጅቶች ጠየቁ