
About
-የጀርመን መራሔ መንግሥት ፍሪድሪሽ ሜርስ ሥደተኞችን የሚያጥላላ መልዕክት ማስተላለፋቸዉ የቀሰቀሰዉ ቁጣና ተቃዉሞ እንደቀጠለ ነዉ።የሜርስን መግለጫ፣ ፖለቲከኞች፣ የመብት ተሟጋቾችና የኤኮኖሚ ባለሙያዎች ነቅፈዉታል።--የሩሲያ ጦር ኃይል የኑክሌር ጦር መሳሪያ ልምምድ ጀመረ።ልምምዱ የኑኬሌር አረር መሸከም የሚችሉ ሚሳዬሎችን፣ መርከቦችንና አዉሮፕላኖችን ያካተተ ነዉ።---የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቢኒያሚን ኔታንያሁ እስራኤል በዩናይትድ ስቴትስ ቁጥጥር ሥር የምትገኝ ሐገር አይደለችም አሉ።ኔታንያሁ የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝደንትን ከማነጋገራቸዉ በፊት ዛሬ እንዳሉት እስራኤል የራስዋን ፀጥታ በሚመለከት የምትወስነዉ ራስዋ ናት።