የታኅሣሥ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
22 December 2025

የታኅሣሥ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) በትግራይ ክልል መጠለያ ውስጥ የሚገኙ ወገኖች ለረሀብ መጋለጣቸውን አመለከተ። በረሀብ ላይ ለሚገኙት ወገኖች መንግሥትን ጨምሮ ሁሉም አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ እንዳለበት፤ የተፈናቀሉትም ወደ የቀያቸው መመለስ እንዳለባቸውም አሳስቧል።

የናይጀሪያ መንግሥት በቅርቡ ታግተው ከነበሩ የቀሩትን 130 ልጆች ማስለቀቁን አስታወቀ። በዛሬው ዕለት ቤተሰቦቻቸውን ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በዛሬው ዕለት በሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በተከሰተ የቦምብ ፍንዳታ አንድ የሀገሪቱ ጀነራል ተገደሉ።

ኢራን የሚሳኤል መርኀግብሯ መከላከያ እና የሚቃጣባትን ጥቃት ለማስቆም የተነደፈ መሆኑን አሳሰበች።