የታኅሳስ 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና
19 December 2025

የታኅሳስ 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼክ ማሕሙድ በአዲስ አበባ ተገናኙ። በኢትዮጵያ ለስደተኞች የሚደረገው ድጋፍ ከውድቀት አፋፍ እንደሚገኝ መንግሥት እና አራት ድርጅቶች አስጠነቀቁ። በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ ሊባባስ እንደሚችል የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ባልደረባ ሥጋታቸውን ገለጹ። ስዊድን በኤርትራ ላለፉት 24 ዓመታት በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ዳዊት ይስሐቅ በሕይወት እንዳለ ገለጸች። የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የሌሎች ሀገር ዜጎች ቋሚ የአሜሪካ የመኖሪያ ፈቃድ በዕጣ የሚያገኙበትን የዲቪ ሎተሪ ፕሮግራም ሊያቆም ነው።