የሰኔ 17 ቀን 2018 የዓለም ዜና
24 June 2026

የሰኔ 17 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
-ራሱን የሊቢያ «የመረጋጋት መንግሥት» ብሎ የሚጠራዉ የምሥራቅ ሊቢያ ስብስብ የኢትዮጵያ፣ የሶማሊያ፣ የኤርትራና የሱዳን ዜጎች ሊቢያ እንዳይገቡ አገደ።---አዉሮጳን የገለበዉ የሙቀት ማዕበል የሰዎች ሕይወት እያጠፋ፣የትምሕርት ሒደት፣ሥራና እንቅስቃሴንም እያስተጓጎለ ነዉ።አለቅጥ የናረዉ ሙቀት ያንገበገባቸዉ አንዳድ ሰዎች ዘለዉ ወንዝ፣ኩሬና ገንዳ ዉስጥ እየገቡ ሞተዋል።--የዓለም የአዉቶሚክ ተቆጣጣሪ ድርጅት (IAEA) የኢራንን የኑክሌር ተቋማትና ንጥረ ነገር በቅርቡ እንደሚፈትሽ አስታወቀ።ኢራን ግን የኑክሌር ጉዳይ የሚነሳዉ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ያደረገችዉ ሥምምነት ገቢራዊነት ሲረጋገጥ ብቻ ነዉ ትላለች።