የሰኔ 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና
17 June 2026

የሰኔ 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
-የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያስገነባችዉ ግድብ ግብፅን ለብዙ ችግሮች አጋልጧል አሉ።ትራምፕ የግብፅ አቻቸዉን ዛሬ ሲያነጋግሩ እንዳሉት መስተዳድራቸዉ ሁለቱን ሐገራት ለማግባባት እንደሚጥር አስታዉቀዋልም።---በ13 ሐገራት ወይም ግዛቶች የሚኖር በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ አስቸኳይ ርዳታ ካላገኘ ለአስከፊ ረሐብ እንደሚጋለጥ የተባበሩት መንግሥታት ሁለት ድርጅቶች አስታወቁ።ድርጅቶቹ እንደሚሉት ሱዳን፣ ሶማሊያና ጋዛን ጨምሮ ለችግር የተጋለጡ 266 ሚሊዮን ሰዎች በቂ ርዳታ አያገኙም።---የቡድን 7 አባል ሐገራት መሪዎች በማደግ ላይ ባሉ ሐገራት ላይ ያለዉን ዕዳ ለማቃለል ቃል ገቡ።