የነሐሴ 28 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜና
03 September 2025

የነሐሴ 28 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ድባጢ ወረዳ በሚገኝ ገጠራማ ስፍራ በዛሬው ዕለት በታጣቂዎች እና መንግሥት ኃይሎች መካከል በተከሰተ ግጭት አራት ታጣቂዎች ሲገደሉ፤ የአንድ ጸጥታ ኃይል ሕይወት ማለፉ ተሰማ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ የነበሩት አቶ ማሞ ምሕረቱ ሥራቸውን መልቀቃቸውን አመለከቱ።

ሱዳን ዳርፉር ግዛት ውስጥ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የሞቱት ከአንድ ሺህ በላይ ሰዎች እንደሚሆኑ ተነገረ።

የቀድሞው የዴሞክራቲክ ኮንጎ የፍትህ ሚኒስትር የግንባታ ፕሮጀክት ገንዘብ በማጭበርበር የሦስት ዓመት እስራት ተፈረደባቸው።