Skip to content
Opens in a new window
የነሐሴ 12 ቀን 2018 የዓለም ዜና
18 August 2026

የነሐሴ 12 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
-የኢትዮጵያ የፈደራል መንግስት ጦር መቀሌ አጠገብ የሚገኝ ሥፍራን ዛሬ በሰዉ አልባ አዉሮፕላን ደብድቧል በማለት ህወሓት ወቀሰ።ህወሓት በድብደባዉ ሥለደረሰዉ ጉዳት አልገለፀም።አንድ የዓይን ምስክር ግን ቢያንስ አንድ ታጣቂ መገደሉንና ሌሎች ሁለት መቁሰላቸዉን አስታዉቀዋል።---የዩናይትድ ስቴትስ የፌደራል ፍርድ ቤት ለኢትዮጵያዉያን የተሰጠዉ አሜሪካ የመኖርና የመሥራት ጊዚያዊ ፈቃድ እንዲሰረዝ ወሰነ።--የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረግም፣ ሊደረግ የታቀደም ድርድር የለም አሉ።የኢራን ባለሥልጣናት እንደሚሉት ግን ዩናይትድ ስቴትስ የገባችዉን ግዴታ ካላከበረች ሥልታዊዉ ወሽመጥ አይከፈትም።