የማክሰኞ ነሐሴ 27 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
02 September 2025

የማክሰኞ ነሐሴ 27 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
አርዕስተ ዜና

«ዓረና ትግራይ ለሉአላዊነት እና ዴሞክራሲ» ፓርቲ ትግራይ ክልል የሽግግር መንግሥት በአስቸኳይ እንዲመሰረት ጥሪ አቀረበ ።

በአማራ ክልል፤ በዋግ ኸምራ ዞን አስተዳደር በረዶ እና ጎርፍ ብርቱ ጥፋት ማድረሱ ተገለጠ ።

የርስ በርስ ጦርነት ባዳቀቃት ሱዳን ውስጥ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ በርካታ የጦርነት ተፈናቃዮችን ጨምሮ ከ1,000 በላይ ሰዎች ሕይወት አለፈ ።

አፍጋኒስታንን አናውጦ ከ1,400 በላይ ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈው ብርቱ ርእደ-መሬት «በመቶ ሺህዎች ላይ» ተጽእኖውን እንደሚያሳርፍ ተጠቀሰ ። እስካሁን ቢያንስ 3251 ሰዎች ላይ የመቁሰል አደጋ መድረሱ ተዘግቧል ።