የመጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
27 March 2026

የመጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል "አስቻይ ኹኔታ እስኪፈጠር" የክልሉን አጀንዳ የማሰባሰብ እና የምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች ልየታን በአዲስ አበባ ለማካሄድ መገደዱን አስታወq።። ኮሚሽኑ እንዳለው ምክክሩ ከመጋቢት 23 እስከ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።

ለአፍሪቃ ሀገራት የተላኩ የኮሌራ መከላከያ መድኃኒቶችና ቁሳቁሶች በኢራን ጦርነት ምክንያት ወደሚፈለጉበት ሀገራት መድረስ አለመቻላቸው ተዘገበ። መድኃኒቶቹ ች ዱባይ በሚገኝ መጋዘን ተከማችተው እንደሚገኙተገልጿል ።

ዛሬ በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል ለማለፍ የሞከሩ ሁለት እቃ ጫኝ የቻይና መርከቦች በሰርጡ ሳያልፉ ተመልሰዋል።