
About
-ታንዛኒያ ዉስጥ ባለፈዉ መስከረም የተደረገዉን አወዛጋቢ ምርጫ በሚቃወሙ የሐገሪቱ ዜጎች ላይ የተፈፀመዉ ግድያ እንደሚጣራ የሐገሪቱ ፕሬዝደንት አስታወቁ።ፕሬዝደንት ሳሚያ ሱሉሑ ሐሰን ዛሬ እንዳሉት የምርጫዉን ሒደት በመቃወማቸዉ ለታሰሩ ሰዎችም መንግሥታቸዉ ምሕርት ያደርጋል።-አፍሪቃ ዉስጥ በተገባደደዉ የግሪጎሪያኑ 2025 ዓመት የተሰራጨዉ የኮሌራ በሽታ 7ሺሕ ሰዎች ገደለ፤ ከ300 ሺሕ በላይ ለከፈ።-የሩሲያና የዩክሬን ጦር ኃይላት ዛሬ አንዱ የሌላዉን ግዛት በሰዉ አልባ አዉሮፕላንና በሚሳዬል ሲደበድቡ አነጉ።