የህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
05 December 2025

የህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
የህዳር 26 ቀን አርዕስተ ዜና

ዛሬ ያስቻለው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት፣ በቀድሞው የሰላም ሚኒስቴር ሚንስትር ድኤታ አቶ ታዬ ደንደአ ላይ የ ሰባት ዓመት ከሁለት ወራት ጽኑ እስራት ፈረደ። የአምስት ሺህ ብር መቀጮም ወሰነ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ ኢህአፓ አቅዶ የነበረው ህዝባዊ ስብሰባ መስተጓጎሉን አስታወቀ። የፓርቲውት ስብሰባው የተስተጓጎለው ገዢው ፓርቲ ባሳደረው ጫና ምክንያት ነው ሲል ዛሬ ለዶቼ ቬለ ተናግሯል።

የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በ23ተኛው የሩስያ ህንድ ጉባኤ የሁለቱን ሀገራት ንግድ ለማስፋትና ለማብዛት ተስማሙ።