የህዳር 19 ቀን 2018 ዓም የዓለም ዜና
28 November 2025

የህዳር 19 ቀን 2018 ዓም የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
የህዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና

ትናንት በመቀሌ ከተማ በአዲ ሃቂ ክፍለ ከተማ የቦምብ ጥቃቱ መፈጸሙን ነዋሪዎች እና የጸጥታ ባለስልጣናት አስታወቁ። ጥቃቱ ስማቸው ያልተጠቀሰ የሰላም እና የፀጥታ ኃላፊ መኖሪያ ቤት ላይ ያነጣጠረ ሳይሆን አይቀርም ሲሉ አንድ የከተማዋ ነዋሪ ለዶቼቬለ ተናግረዋል።

የምዕራብ አፍሪቃ አገራት የኤኮኖሚ ማኅበረሰብ ኤኮዋስ መፈንቅለ መንግሥት የተካሄደባትን ጊኒ ቢሳውን ከውሳኔ ሰጭ አካልነት እንደሚያግድ አስጠነቀቀ።


የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሦስተኛው ዓለም ሀገራት ወደ አሜሪካን የሚሰደዱ ሰዎች በሙሉ ወደ አሜሪካን መግባታቸውን እንደሚያስቆሙ አስታወቁ።