የዓለም ዜና፤ ጥር 12 ቀን 2018 ማክሰኞ
20 January 2026

የዓለም ዜና፤ ጥር 12 ቀን 2018 ማክሰኞ

የዓለም ዜና

About
--የአውሮጳ ህብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኡርሱላ ፎን ደር ሌየን ህብረቱ ግሪንላንድ ውስጥ “ግዙፍ” መዋዕለ ንዋይ ለማፍሰስ ማቀዱን ተናገሩ። ኮሚሽነርዋ ይህን የተናገሩት ትራምፕ የአርክቲክ ውቅያኖስ ደህንነትን ለማስጠበቅና ግሪንላንድን ለመጠቅለል ዛቻ እያደረሱ ባለበት በአሁኑ ወቅት ነዉ።--የግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ ኧል ሲሲ ዳቮስ ስዊዘርላንድ ላይ እየተካሄደ ባለዉ የዓለም ኤኮኖሚ ጉባኤ ጎን ለጎን ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ተገናኝተዉ እንደሚነጋገሩ አስታወቁ።--ሩሲያ በዩክሬይን መዲና ኪየቭ ላይ ባደረሰችዉ የአየር ላይ ጥቃት በሺዎች የሚቆጠሩ የመኖሪያ ህንፃዎች የኤሌትሪክ ኃይልና የውኃ አቅርቦት ተቋረጠ።