
About
--የአውሮጳ ህብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኡርሱላ ፎን ደር ሌየን ህብረቱ ግሪንላንድ ውስጥ “ግዙፍ” መዋዕለ ንዋይ ለማፍሰስ ማቀዱን ተናገሩ። ኮሚሽነርዋ ይህን የተናገሩት ትራምፕ የአርክቲክ ውቅያኖስ ደህንነትን ለማስጠበቅና ግሪንላንድን ለመጠቅለል ዛቻ እያደረሱ ባለበት በአሁኑ ወቅት ነዉ።--የግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ ኧል ሲሲ ዳቮስ ስዊዘርላንድ ላይ እየተካሄደ ባለዉ የዓለም ኤኮኖሚ ጉባኤ ጎን ለጎን ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ተገናኝተዉ እንደሚነጋገሩ አስታወቁ።--ሩሲያ በዩክሬይን መዲና ኪየቭ ላይ ባደረሰችዉ የአየር ላይ ጥቃት በሺዎች የሚቆጠሩ የመኖሪያ ህንፃዎች የኤሌትሪክ ኃይልና የውኃ አቅርቦት ተቋረጠ።