
About
-በአሜሪካና በዩክሬን መካከል ፍሎሪዳ በተካሄደዉ ውይይት ተስፋ እንዳላቸዉ ትራምፕ ገለፁ።-በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ባቲ ወረዳ ላለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት መፍትሔ አጥቶ የዘለቀዉ ግጭት በሽምግልና ስርአት መቋጨቱ ተነገረ።-ደቡባዊ ኢትዮጵያ ውስጥ በተከሰተው የማርበርግ ቫይረስ የስምንት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።-ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሚቀጥለዉ በቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ ደቡብ አፍሪቃ አትጋበዝም ማለታቸዉን ራማፎሳ ውድቅ አደረጉ።-በዓለም ዙርያ በርካታ ግጭቶች በሚካሄዱበት በአሁኑ ወቅት የጦር መሳሪያ ኢንዱስትሪዉ ከፍተኛ የጦር መሳርያ ንግድ ገቢን ማስመዝገቡ ተዘገበ።