DW Amharic የየካቲት 07 ቀን 2018 የዓለም ዜና
14 February 2026

DW Amharic የየካቲት 07 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
በአፍሪካ “ግልጽ እና ድብቅ ግጭቶች ሥር እየሰደዱ” መምጣታቸውን “ሕገ-መንግሥታዊ ያልሆኑ የመንግሥት ለውጦች” ማንሠራራታቸውን የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ማሕሙድ አሊ ይሱፍ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ኢትዮጵያ የባሕር በር ልታገኝ ይገባል የሚል አቋማቸውን ለ39ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ገልጸዋል።
ስድስት የግል ባንኮች ድርሻዎቻቸውን በካፒታል ገበያ ለማስመዝገብ መቃረባቸውን የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ይፋ አደረገ። የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት ጆንጊሌ እና ምሥራቅ ኢኳቶሪያ ግዛቶችን ጨምሮ በመላ ደቡብ ሱዳን ግጭት መባባሱ እጅግ እንዳሳሰበው አስታወቀ።