DW Amharic የነሐሴ 25 ቀን 2017 የዓለም ዜና
31 August 2025

DW Amharic የነሐሴ 25 ቀን 2017 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
መሐመድ ሐምዳን ደጋሎ የሱዳን ትይዩ መንግሥት መሪ ሆነው መሐላ ፈጸሙ። የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ ቃል አቀባይ አቡ ኡቤይዳ በጋዛ መገደላቸውን የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ገለጹ። ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ ዩክሬን በሩሲያ ውስጥ ጥቃት ለመፈጸም ዕቅድ እንዳላት ተናገሩ። የሩሲያ መከላከያ ሚኒስትር ቫለሪ ጌራሲሞቭ ሀገራቸው ከመስከረም እስከ ሕዳር ተግባራዊ የሚሆን የጥቃት ዕቅድ ማዘጋጀቷን አስታውቀዋል። የቻይና እና የሕንድ መሪዎች በድንበር ይገባኛል የገቡበትን እሰጥ አገባ በመፍታት ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ። ኢትዮጵያዊው ኃይለማርያም ኪሮስና ኔዘርላንዳዊቷ ሲፋን ሐሰን በሲድኒ ማራቶን የቦታውን ክብረ-ወሰን በማሻሻል አሸነፉ።