DW Amharic የመጋቢት 22 ቀን 2018 የዓለም ዜና
31 March 2026

DW Amharic የመጋቢት 22 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
አሜሪካ እና እስራኤል ከኢራን በገጠሙት ጦርነት ምክንያት ለኢትዮጵያ ነዳጅ የሚያቀርቡ ሀገራት በውላቸው መሠረት ማቅረብ እንደማይችሉ ማሳወቃቸውን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ተናገሩ። የሶማሊያ ጦር የደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ ግዛት ትልቅ ከተማ የሆነችው ባይዶዋን ተቆጣጠረ። እስራኤልና ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነትና የኢራን አፀፋ የመካከለኛዉ ምሥራቅ ሐገራትን ማዉደሙን ለሁለተኛ ወር እንደቀጠለ ነዉ። ጦርነቱ እንዲቆም ፓኪስታን እና ቻይና ጠይቀዋል እስራኤል በጦር ፍርድ ቤቶች ጥፋተኛ የተባሉ ፍልስጤማውያን ሁሉ በስቅላት እንዲቀጡ ያጸደቀችው ሕግ እጅግ አሳሳቢ እንደሆነ የአውሮጳ ኅብረት ኮሚሽን ሥጋቱን ገለጸ።