DW Amharic የመጋቢት 20 ቀን 2018 የዓለም ዜና
29 March 2026

DW Amharic የመጋቢት 20 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
የሶማሊያ ፌድራል መንግሥት እና የደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ ግዛት በመካከላቸው የተፈጠረውን ውጥረት ከማባባስ እንዲቆጠቡ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ማሕሙድ አሊ ይሱፍ አሳሰቡ። አሜሪካና እስራኤል ከኢራን የሚያካሒዱት ውጊያ የሚቆምበት ሁኔታ ላይ ለመወያየት የቀጠናው ቁልፍ ሀገራት ከፍተኛ ዲፕሎማቶች በፓኪስታን ተሰበሰቡ። ጦርነቱ ዓለም አቀፍ ሕግ እንደሚጥስ ቡንደስታግ ተብሎ የሚጠራው የጀርመን ምክር ቤት የምርምር አገልግሎት ይፋ ያደረገው ሪፖርት አሳየ። በአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕና ፖሊሲዎቻቸውን ለመቃወም በተለያዩ ከተሞች በተካሔዱ ሰልፎች ቢያንስ 8 ሚሊዮን ሰዎች ተሳትፈዋል ተብሎ እንደሚገመት አዘጋጆቹ አስታወቁ።