DW Amharic የኅዳር 21 ቀን 2018 የዓለም ዜና
30 November 2025

DW Amharic የኅዳር 21 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
በጦርነት የምትታመሰው ሱዳን “የገጠሟትን ከባድ ፈተናዎች ለማሸነፍ የምታደርገውን ጥረት” ኤርትራ መደገፏን እንምትቀጥል ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለጠቅላይ ሚኒስትር ከማል ኢድሪስ በድጋሚ አረጋገጡ። በደቡብ ምሥራቅ እስያ ሦስት ሀገራት የጣለ ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር ከ600 በላይ ደረሰ። በእስራኤል ወታደራዊ ዘመቻ የተገደሉ ፍልስጤማውያን ቁጥር ከ70,000 እንደበለጠ የጋዛ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ለቀረበባቸው የሙስና ክስ የይቅርታ ጥያቄያቸውን ለሐገሪቱ ፕረዚደንት አቀረቡ።