
22 January 2026
"ጥምቀት ከፍተኛ የሆነ ምስጢር ያለው፣ የስላሴ ሶስትነት፣ አንድነት የተገለፀበት፤ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ጋር የተወለደበት ሙሉ የሆነበት ነው" ቀሲስ መንግሥቱ ኃይሉ
SBS Amharic - ኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ
About
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዓመታዊው በዓለ ጥምቀት በሀገረ አውስትራሊያ - ብሪስበን ከተማ በ Oxley Creek Common ከጃኑዋሪ 24 - 25 / ጥር 16 - 17 ተከብሮ ይውላል። ቀሲስ መልአከ ፀሐይ መንግሥቱ ኃይሉ፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የምሥራቅ አውስትራሊያና ኒውዝላንድ አኅጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅና በብሪስበን የደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ፤ እንዲሁም አቶ ወርቅነህ ባየህ፤ በብሪስበን የደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ስለ በዓሉ መሰናዶ፣ መርሃግብርና የበዓለ ጥምቀትን ተምሳሌነትና ፋይዳዎች ያስረዳሉ።