
05 March 2026
"በጄሲ ጃክሰን የምርጫ ዘመቻ ወቅት ትልቅ አስተዋፅዖ አደረግኩ የምለው፤ዜግነት የሌላቸውም አስተዋፅዖ እንዲያደርጉ ያቀረብኩት ሃሳብ ውጤታማ መሆኑ ነው"የሐረርወርቅ ጋሻው
SBS Amharic - ኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ
About
የፖለቲካ አንቂ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ቀስቃሽ፣ የቀድሞው የዲሞክራት ፓርቲ የሁለት ዙር ዕጩ ፕሬዚደንት ጄሲ ጃክሰን የወጣቶች ኮሚቴ ሰብሳቢና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች አማካሪ ወ/ሮ የሐረወርቅ ጋሻው፤ ፌብሪዋሪ 17 ቀን 2026 ከእዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት ጄሲ ጃክሰን ፕሬዚደንታዊ የምርጫ ዘመቻ ወቅት ስላበረከቷቸው አስተዋፅዖዎች አንስተው ይናገራሉ። የጃክሰንን ሰብዓዊ ገፅታም ይዘክራሉ።